ኢትዮጵያ በአረንጓዴ አሻራ መርኃ ግብር ለበርካታ ሀገሮች ምሳሌ መሆን ችላለች

በአረንጓዴ አሻራ መርኃ ግብር ኢትዮጵያ ለበርካታ ሐገሮች ምሳሌ መሆን መቻሏን የኢትዮጵያ ደን ልማት ዋና ዳይሬክተር አቶ ከበደ ይማም ገለፁ፡፡ የመሬት መራቆት እና የአየር ንብረት ለውጥ በስነ ምህዳር ላይ አሉታዊ ተዕፅኖ እየሳረፈ በመሆኑ መንግስታት እርምጃ መውሰድ እንዳለባቸው ያነሱት ዋና ዳይሬክተሩ፤ በየአመቱ የሚሰሩ ብዙ ጥናቶች በጉዳዩ ላይ ትኩረት አድርገው ሰፊ መረጃዎችን እንደሚያወጡም ገልፀዋል፡፡ በዚህ ረገድ ኢትዮጵያ ለጉዳዩ የሰጠችው ትኩረት በአረንጓዴ አሻራ መርኃ ግብር ለበርካታ ሀገሮች ምሳሌ እንድትሆን ያስቸላት መሆኑን ተናግረዋል፡፡ አያይዘውም መንግስት ለተራቆቱ አከባቢዎች ማገገሚያ የሚውል ፈንድ ማፅደቁን ተከትሎ የደን ጭፍጨፋው ወደ 27 ሺህ ሔክታር መሬት ዝቅ ማድረግ መቻሉን አንስተዋል፡፡ ዋና ዳይሬክተሩ…

Read More

የአረንጓዴ አሻራ የደን ሸፋን ከማሳደግ በላይ… – Ethiopian Broadcasting Corporation | Facebook

የአረንጓዴ አሻራ ከደን ሸፋን ማሳደግ በላይ መሆኑን በኢቲቪ ዳጉ የውይይት መርሐ ግብር ላይ እንግዳ የነበሩት የኢትዮጵያ ደን ልማት ዋና ዳሬክተር አቶ ከበደ ይማም ገልጸዋል። አረንጓዴ አሻራ እንደ ሀገር ጠንካራ ኢኮኖሚ የመገንባት እንዲሁም ጠንካራ ሀገረ መንግስት የመገንባት መሰረትም ነው ብለዋል። አረንጓዴ አሻራ የተራቆቱ መሬቶችን እንዲያገግሙ ከማድረግ ባሻገር በሀገር ኢኮኖሚ ላይ ሰፊ የሆነ ድርሻ እንዳለው ያነሱት ዳይሬክተሩ፤ ለሀገር ሉዓላዊነት ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንዳለውም ጠቅሰዋል። “የተራቆቱ መሬቶችን እንዲያገግሙ ማድረግ ካልቻልን፤ የምናልመው ምርታማነት አይኖርም፣ ብዝኃ ህይወት ያልቃል ብሎም እንደ ውኃ ያሉ ተፈጥሯዊ ሀብቶቻችን ይቀንሳሉ፤ ይህም በሂደት አስከፊ ለሆነ ችግር ይዳርገናል” ብለዋል ዋና ዳይሬክተሩ። ኢትዮጵያ ላለፉት…

Read More

Lawmakers ratify Green Legacy, degraded land rehabilitation special fund proclamation

On Dec 24, 2024 207 Addis Ababa, December 24, 2024 (FMC) –– Ethiopia’s House of People’s Representatives (HoPR) has unanimously passed a proclamation for the establishment and administration of the Green Legacy initiative and degraded land rehabilitation special fund. This move is expected to enhance Ethiopia’s collaboration and benefits from development partners in the forestry sector. During its 12th regular session of the 4th year held today, the 6th HoPR passed the bill as Proclamation No. 1361/2017. It is worth noting that the draft proclamation for the special fund for the Green…

Read More

የአረንጓዴአሻራ የተጎዱ መሬቶች ማገገሚያ ፈንድ

በኢፌዲሪ የኢትዮጵያ ደን ልማት Ethiopian Forestry Development-EFD Favorites · 2h · #የአረንጓዴአሻራ የተጎዱ መሬቶች ማገገሚያ ፈንድ See Translation Amhara Media Corporation/ አማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን 4h · የጸደቀው ረቂቅ አዋጅ የተጎሳቆሉ አካባቢዎችን በደን ልማት መልሰው እንዲያገግሙ ያደርጋል። አዲስ አበባ: ታኅሣሥ 16/2017 ዓ.ም (አሚኮ) የኢትዮጵያ ደን ልማት ትናንት ታኀሣሥ 15 2017 ዓ.ም የጸደቀውን የአረንጓዴ አሻራ እና የተጎሳቆለ መሬት ማገገሚያ ልዩ ፈንድ ማቋቋሚያ እና አሥተዳደር ረቂቅ አዋጅን አስመልክቶ መግለጫ ሰጥቷል። የኢትዮጵያ ደን ልማት ዋና ዳይሬክተር ከበደ ይማም የጸደቀው ረቂቅ አዋጅ በኢትዮጵያ የተጎሳቆሉ አካባቢዎችን በደን ልማት እና በጥምር ደን ግብርና መልሰው እንዲያገግሙ ያደርጋል ብለዋል። ከፍተኛ የኾነ ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ…

Read More

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የአረንጓዴ አሻራና የተጎሳቆለ መሬት ማገገሚያ ልዩ ፈንድ ማቋቋሚያና አስተዳደር አዋጅን አጸደቀ

Ministry of Agriculture – Ethiopia (አዲስ አበባ፣ ታኀሳስ 15 ቀን 2017 ዓ.ም፣ ግብርና ሚኒስቴር) የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብርን ውጤታማ በሆነ መልኩ ያስችላል የተባለውን የአረንጓዴ አሻራና የተጎሳቆለ መሬት ማገገሚያ ልዩ ፈንድ ማቋቋሚያና አስተዳደር ረቂቅ አዋጅን በሙሉ ድምፅ አጸደቀ። በምክር ቤቱ 12ኛ መደበኛ ስብሰባ የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ደሳለኝ ወዳጆ አዋጁን የተመለከተ ሪፖርትና የውሳኔ ሀሳብ አቅርበዋል። አዋጁ በኢትዮጵያ የተጀመረውን የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር ውጤታማና ቀጣይነት ባለው መልኩ ለመምራት በልዩ ፈንድ እንዲደገፍ የሚያስችል መሆኑ ተጠቅሷል። አቶ ደሳለኝ ባለፉት ስድስት ዓመታት የተጀመረው የአረንጓዴ አሻራ የተጎሳቆለ መሬት እንዲያገግም ከማድረግ…

Read More